No Touching

Date posted: Tuesday, March 24, 2020



የእኛ ሀገር የኑሮ ሁኔታ ማህበራዊ ርቀትን በቶሎ ለመተግበር አስቸጋሪ ቢሆንም የቫይረሱ ስርጭት ከሚያደርሰው የከፋ ጉዳት ለመትረፍ ግን የጤና ባለሞያዎችን ምክር መስማት ግዴታ ነው። መንግስትም በቻለው አቅም ጊዜው #ሳይረፍድ የተሻሉ አማራጮችን ቢፈልግ መልካም ነው። ፎቶው አሁን መገናኛ አካባቢ ያለውን ሁኔታ የሚያሳይ ነው።

እኛ የጤና ባለሞያዎች የሚሉንን ካላዳመጥን፣ የምንባለውን ካልተገበርን ፣ ቸልተኝነታችን ነገ ሳይሆን አሁን ካልተገታ ፣ አታድርጉ የምንባለውን ከማድረግ ካልተቆጠብን ፣ በምን አይነት መልኩ ነው ይህን ቫይረስ ምንቋቋመው ?

የግድ ለመጠንቀቅ ብዙ ሺ ሰው መታመም አለበት ? ሌሎች ያዩትን መከራ ማየት አለብን? ለመጠንቀቅ ሰው መሞት አለበት? ኮሮና ቫይረስ ቀልድ አይደልም! የምንባለውን ካላዳመጥን ፤ የሚባለውን ካልተገበርን ጣልያን እየሆነች እንዳለው መሆናችን አይቀርም።

እጅግ በጣም ቀላል የሆኑ የቫይረሱን የመከላከያ መንገዶችን በመዘናጋት ፣ በፌዝ ፣ በቀልድ እያየን የማንወጣው አዘቅት ውስጥ እንዳንገባ አደራ። አትፍሩ ማለት አትጠንቀቁ ማለት አይደለም! በሲያንስ ለሌሎች ወገኖች እናስብ !

ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኝላችኃለን!
ሰላም እደሩ!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia




Testimony


"It is really commendable institution deep rooted in the heart of in the center of the national NBCH interventions having strong and close partnership with us, This institution continue serving the community appropriately everlastingly."
1 / 2
"የብሄራዊ ህጻናት ጤና ቡድን ዋና አጋር የሆነው የኢትዮጵያ ህጻናት የህክምና ማህበር በታለያዩ የሥራ ዘርፎች በተላም ደግሞ የባለሙያዎችን አቅም በመገንባት አዳዲስ መረጃዎችን በጥናትና ምርምር በማፍለቅ ፤ የቴክኒካል ዎርኪንግ ግሩፕ ዋና አውታር በመሆን የሚዘጋጁ ዶክመንቶችን ስናዘጋጅ አዳድስ ሳይንተፊክ ኢቪደንሶችን መማጣት እጅግ በጣም እያገዘን ያለ ተቋም ነው፤፤"
2 / 2






e-learning
© Ethiopian Pediatrics Society 1995-2024. All Rights Reserved.
All trademarks displayed in this web site are the exclusive property of the respective holders.